Membership Registration

የአባልነት ምዝገባ

Membership Registration

የአባልነት ምዝገባ

Welcome, and thank you for your desire to become a member of St. Mary Ethiopian Orthodox Tewahedo Church. Membership in the Church is a sacred commitment to grow in faith, participate in the life of the Church, and live according to the teachings of our Lord Jesus it is written in Psalm 133:1, "How good and pleasant it is when God’s people live together in unity!" By completing this form, you are expressing your willingness to join our church family, take part in worship, and support the mission of the Church. We are many members, but as Romans 12:5 reminds us, "In Christ we, though many, form one body, and each member belongs to all the others."We invite you to uphold the faith and traditions of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church, as we strive together to be "rooted and built up in Him, strengthened in the faith as you were taught, and overflowing with thankfulness" (Colossians 2:7).May God bless you as you take this important step in your spiritual journey.Registration ChecklistTo complete your official registration, please ensure you have the following ready:Family Details: Full names and ages for spouses and children under 21.Contribution: Select your monthly stewardship level (starting from $10).Photo: A family photo for the church records (optional but encouraged).Signature: Your digital agreement to uphold the Tewahedo faith and traditions."Each of you should use whatever gift you have received to serve others, as faithful stewards of God’s grace." — 1 Peter 4:10

የአባልነት ምዝገባ

እንኳን ወደ ቅድስት ማርያም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአባልነት ምዝገባ በደህና መጡ። በቤተ ክርስቲያን አባል መሆን ከሚጠቅመን ዋና ዋና ነገሮች አንዱ በእምነት ለማደግ፣ በቤተ ክርስቲያን ሕይወት ውስጥ ለመሳተፍ እና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ትምህርት መሠረት ለመኖር እንድንችል ስለሚረዳን እና እኛም በአባልነታችን በምናደርጋቸው አገልግሎቶች የሰማያዊ በረከት ተሳታፊ ስለሚያደርገን ጭምር ነው ይህ ደግሞ መንፈሳዊ መታደልነው።

አምላካችን እግዚኣብሔር አስቀድሞ ቅዱስ ዳዊት እንደተናገረ በመዝሙር 133:1 ላይ "ወንድሞች በኅብረት ቢቀመጡ እነሆ፥ መልካም ነው፥ እነሆም፥ ያማረ ነው!" ተብሎ እንደተጻፈ፤ እርስዎም ይህንን ቅጽ በመሙላት የቤተ ክርስቲያናችን ቤተሰብ አባል ለመሆን፣ በአምልኮ ለመሳተፍ እና የቤተ ክርስቲያኒቱን ተልእኮ ለመደገፍ ያለዎትን ፈቃደኝነት ይገልጹ ዘንድ መንፈሳዊ ጥሪያችነን እናቀርብልዎታለን።

ሐዋርያምው ቅዱስ ጳውሎስ እንዳስተማረን በቤተ ክርስቲያን አንድነት ጉባዔ ስንሳተፍና ህብረት ሲኖረን ይህ አንድነትና ህብረት ከአምላካችን ከእየሱስ ክርስቶስ ጋር አንድ የሚያደርግ ነው ፣ ሮሜ 12:5 "እንዲሁ እኛ ብዙዎች ስንሆን በክርስቶስ አንድ አካል ነን፥ እርስ በርሳችንም እያንዳንዳችን የሌላው ብልቶች ነን።"

በእምነት "ሥር ሰዳችሁና ታንጻችሁ፥ እንደ ተማራችሁትም በእምነት ጸንታችሁ፥ ምስጋናም ይብዛላችሁ" (ቆላስይስ 2:7) ተብሎ እንደተጻፈው ሁሉ፤ እያንዳንዳችን በዚህ የመመዝገቢያ ቅጽ ተመዝግባችሁ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን እምነትና ትውፊት እንድትጠብቁ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

የምዝገባ ቅድመ-ሁኔታዎች (Checklist)

ይፋዊ ምዝገባውን ለማጠናቀቅ እባክዎ የሚከተሉት ዝግጁ መሆናቸውን ያረጋግጡ፦

የቤተሰብ ዝርዝር፦ የትዳር አጋር እና ዕድሜያቸው ከ21 ዓመት በታች የሆኑ ልጆች ሙሉ ስም እና ዕድሜ።

መዋጮ፦ ወርሃዊ የአባልነት መዋጮ መጠንዎን ይምረጡ (ከ$10 ጀምሮ)።

ፎቶ፦ ለቤተ ክርስቲያን መዝገብ የሚሆን የቤተሰብ ፎቶ (ግዴታ ባይሆንም ይበረታታል)።

ፊርማ፦ የተዋሕዶ እምነትንና ትውፊትን ለመጠበቅ የሚገቡት ዲጂታል ስምምነት።

"እያንዳንዱ እንደ ተቀበለው የጸጋ ስጦታ መጠን እግዚአብሔርን ልዩ ልዩ ጸጋ እንደ ጥሩ መጋቢዎች እርስ በርሳችሁ አገልግሉ" — 1 ጴጥሮስ 4:10

ንኳን ለእመቤታችን የድንግል ማርያም የጾመ ፍልሰታ በሰላም በጤና አደረሰዎት። አምላክ ጾሙን የሰላም፣ የይቅርታና የበረከት ያድርግልን።

የፍልሰታ ጾም አርብ ነሐሴ ፩ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም.Friday, August 7, 2026 ይጀመራል እንደተለመደው በቤተ ክርስቲያናችን እንደ ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እምነትና ሥርዓት ከጧቱ በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ፬ ሰዓት የውዳሴ ማርያም የቅዳሴ ማርያም ትርጓሜ ይደርሳል እኩለ ቀን ፮ ሰዓት ጸሎተ ቅዳሴ ይጀመራል ስለዚህም እርስዎም የበረከቱ ተሳታፊ እንዲሆኑ ኑ ከእመቤታችን በረከትንና ረድዔትን እንሳተፍ ልዩ የሱባዔ ጊዜ ይሁንልዎ።

ነሐሴ ፲፮ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም.Saturday, August 22, 2026 ታቦተ ህጉ ከመንበረ ክብሩ ወጥቶ የዓመት ክብረ በዓል በልዩ ሐይማኖታዊ ሥነ ሥርዓት ይከበራል።

Filseta Fast (Dormition Fast of the Holy Virgin Mary)

The Filseta Fast will begin on Friday, August 7, 2026.

As is our longstanding tradition, St. Mary's Ethiopian Orthodox Tewahedo Church in Los Angeles will observe this holy fast in accordance with the faith, doctrine, and sacred traditions of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church.

Daily Worship Schedule

Monday to Friday

10:00 a.m.
Wudase Mariam (Praises of the Holy Virgin Mary) followed by the explanation and interpretation of the Marian Liturgy.

12:00 p.m. (Noon)
The Divine Liturgy (Holy Qidase) begins.

We warmly invite all the faithful to join us in this blessed season of fasting and prayer to receive the blessings, intercessions, and spiritual grace of our Most Holy Mother, the Ever-Virgin Mary.

May this Filseta Fast be a time of spiritual renewal, repentance, peace, and abundant blessings for you and your family.

saturday and sunday

6:00 a.m. (Morning)
The Divine Liturgy (Holy Qidase) begins.

09:30 am.
Wudase Mariam (Praises of the Holy Virgin Mary) followed by the explanation and interpretation of the Marian Liturgy.

Annual Feast Celebration

On Saturday, August 22, 2026, the Tabot (Ark) of the Covenant will come forth from its holy sanctuary, and the annual feast will be celebrated with the sacred liturgical traditions and solemn religious ceremonies of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church.

Come and share in the blessings and intercessions of our Holy Mother, the Virgin Mary.

St. Mary's Ethiopian Orthodox Tewahedo Church
Los Angeles, California

Announcement/ማስታወቂያ

ንኳን ለእመቤታችን የድንግል ማርያም የጾመ ፍልሰታ በሰላም በጤና አደረሰዎት። አምላክ ጾሙን የሰላም፣ የይቅርታና የበረከት ያድርግልን።